Wednesday 27 March 2013

ባል የአምስት ወር ነፍሰጡር ሚስቱን ገደለ


የአምስት ወር ነፍሰጡር የነበረችውን ባለቤቱን ሆዷ ላይ ስድስት ቦታ በጩቤ ወጋግቶ የገደለው ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ ባልና ሚስቱ ለአራት ዓመታት በጋብቻ ተሳስረው ሲኖሩ የሁለት ዓመት ልጅ አፍርተዋል፡፡ በምዕራብ ጐጃም ቡሬ ከተማ ውስጥ በተፈፀመው በዚህ ወንጀል ከሟች ሌላ የሟች ወ/ሮ ተናኜ ገረም ወላጅ እናትና አባት በጩቤ የመወጋት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ የቡሬ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት መርማሪ የሆኑት ዋና ሳጅና አልማው ደሴ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት ባለፈው ወር መጨረሻ በባልና ሚስት መካከል በተፈፀመ ያለ መግባባት ሚስት ወደ ወላጆቿ ቤት ሄዳ ነበር፡፡

ባል እዚያ ሄዶ ግድያውን መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡ ተጠርጣሪው በትዳር አጋሩ ላይ ይህን ወንጀል በፈፀሙ የአካባቢው ህብረተሰብ ቁጣ ተቀስቅሷል፡፡ ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ መካሄዱን የጠቆሙት ዋና ሳጅን አልማው የምርመራ መዝገቡ ለዐቃቤ ሕግ ተላልፎ ክስ መመስረቱንም ጠቁመዋል፡፡ በተጠርጣሪው በጩቤ የተወጉት የሟች ወላጅ እናትና አባት በአሁኑ ወቅት በህክምና ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል፡፡
source and picture ADDIS ADMAS news paper.

No comments:

Post a Comment